May 15, 2025

አዳማ፣ ግንቦት 8 ቀን 2017 ዓ.ም (ከመልሚ)

በከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት እና ኮሚኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ አዘጋጅነት የተካሄደ የህዝብ ግንኙነት እና የሚዲያ አካላት ፎረም ነው።

በመድረኩ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ፣ ከተጠሪ ተቋማት፣ ከሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም ከሚዲያ ተቋማት የተወጣጡ የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

በመድረኩ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት ያስተላለፉት በከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት እና ኮሚኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ አቶ ኢትዮጵያ በደቻ እንደተናገሩት ፎረሙ በሚዲያ እና በህዝብ ግንኙነት አካላት መካከል ትክክለኛ እና ተገቢ ተግባቦት በመፍጠር መረጃዎችን ለህዝብ ተደራሽ እንዲሆን ሲሰራ እንደነበረ በመግለፅ ዘርፉ በአግባቡ እና በተናበበ መንገድ ካልተመራ ላላስፈላጊ ተግዳሮቶች እንደሚያጋልጥ ተናግረዋል።

የከተማና መሰረተ ልማት ዘርፍ በርካታ ሀገራዊ የልማት ስራዎች የሚከናወኑበት እንደመሆኑ የከተማ ነዋሪዎችም ፍትሃዊ የመልማት  ጥያቄዎች የሚያነሱበት ዘርፍ ነው ። በለላ በኩል ህብረተሰቡን የልማት  አካል በማድረግ  የሚፈለገው መረጃ ለታለመለት ዓላማ ለማዋል የሚዲያው አካል ከፍተኛ ድርሻ ስላለው ስራዎችን በእውቀት እና በመረጃ መስራት እንደሚገባ አያይዘው ተናግረዋል።

መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት በከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የሚኒስቴር ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አባድር ፋሪስ እንዳሉት ይህ መድረክ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በህዝብ ግንኙነት እና ኮሚኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ አዘጋጅነት የሚካሄድ መድረክ እንደመሆኑ መጠን ከሚዲያ አካላት፣ ከተጠሪ ተቋማት እንዲሁም ከእየክልሉ አና ከከተማ አስተዳደሮች የተሳተፋችሁ አካላት እንደመሆናቸው ለሀገር ሰላም ትልቅ አቅም በመሆናችሁ መድረኩን በአግባቡ በመከታተል ለህብረተሰቡ ተደራሽ እንድታደርጉ ሲሉ ተናግረዋል።

በእለቱ በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን እና በኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት የተዘጋጁ ሰነዶች ቀርበው ሰፋ ያለ ውይይት በማድረግ በአቶ ኢትዮጵያ በደቻ የማጠቃለያ ሀሳብ የመድረኩ መርሀ ግብር ተጠናቋል።

ሪፖርተር ኮከቤ ቢፍቱ
የካሜራ ባለሙያ ፈዬ ደሜ

Posted in: News